በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የመዝሙር መጽሐፍ

ምዕራፎች

የመጽሐፉ ይዘት

  • 1

    • ተቃራኒ የሆኑ ሁለት መንገዶች

      • የአምላክን ሕግ ማንበብ ያስደስታል (2)

      • ጻድቃን እንደሚያፈራ ዛፍ ናቸው (3)

      • ክፉዎች ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ገለባ ናቸው (4)

  • 2

    • ይሖዋና እሱ የቀባው ንጉሥ

      • ይሖዋ በብሔራት ላይ ይስቃል (4)

      • ይሖዋ ንጉሡን ይሾማል (6)

      • ልጁን አክብሩ (12)

  • 3

    • አደጋ ቢኖርም በአምላክ መተማመን

      • “ባላጋራዎቼ እንዲህ የበዙት ለምንድን ነው?” (1)

      • “ማዳን የይሖዋ ነው” (8)

  • 4

    • በአምላክ በመታመን የቀረበ ጸሎት

      • “ተቆጡ፤ ሆኖም ኃጢአት አትሥሩ” (4)

      • “በሰላም እተኛለሁ” (8)

  • 5

    • ይሖዋ ለጻድቅ መጠጊያ ነው

      • አምላክ ክፋትን ይጠላል (4, 5)

      • “በጽድቅህ ምራኝ” (8)

  • 6

    • ሞገስ ለማግኘት የቀረበ ልመና

      • ሙታን አምላክን አያወድሱም (5)

      • አምላክ ሞገስ ለማግኘት የሚቀርብን ልመና ይሰማል (9)

  • 7

    • ይሖዋ ጻድቅ ፈራጅ ነው

      • ‘ይሖዋ ሆይ፣ ፍረድልኝ’ (8)

  • 8

    • የአምላክ ክብርና የሰው ክብር

      • ‘ስምህ ምንኛ የከበረ ነው!’ (1, 9)

      • “ሟች ሰው ምንድን ነው?” (4)

      • ‘የግርማ ዘውድ ደፋህለት’ (5)

  • 9

    • የአምላክን ድንቅ ሥራዎች ማወጅ

      • ይሖዋ አስተማማኝ መጠጊያ ነው (9)

      • “ስምህን የሚያውቁ በአንተ ይታመናሉ” (10)

  • 10

    • ይሖዋ ምስኪኑን ይረዳል

      • ክፉ ሰው በትዕቢት “አምላክ የለም” ይላል (4)

      • ምስኪኑ ወደ ይሖዋ ይጮኻል (14)

      • “ይሖዋ ለዘላለም ንጉሥ ነው” (16)

  • 11

    • ይሖዋን መጠጊያ ማድረግ

      • “ይሖዋ ቅዱስ በሆነው ቤተ መቅደሱ ውስጥ ነው” (4)

      • አምላክ ዓመፅን የሚወድን ሰው ይጠላል (5)

  • 12

    • ይሖዋ እርምጃ ለመውሰድ ይነሳል

      • የአምላክ ቃል የጠራ ነው (6)

  • 13

    • የይሖዋን ማዳን መጠባበቅ

      • ‘ይሖዋ ሆይ፣ እስከ መቼ ነው?’ (1, 2)

      • ይሖዋ በእጅጉ ይክሳል (6)

  • 14

    • የሞኝ ሰው መገለጫ

      • “ይሖዋ የለም” (1)

      • “መልካም የሚሠራ ማንም የለም” (3)

  • 15

    • በይሖዋ ድንኳን የሚስተናገድ ማን ነው?

      • በልቡ እውነትን ይናገራል (2)

      • ስም አያጠፋም (3)

      • “ጉዳት ላይ ሊጥለው ቢችልም እንኳ ቃሉን አያጥፍም” (4)

  • 16

    • ይሖዋ የጥሩነት ምንጭ ነው

      • “ይሖዋ ድርሻዬ” ነው (5)

      • ‘በሌሊት በውስጤ ያለው ሐሳብ ያርመኛል’ (7)

      • ‘ይሖዋ በቀኜ ነው’ (8)

      • “መቃብር ውስጥ አትተወኝም” (10)

  • 17

    • ጥበቃ ለማግኘት የቀረበ ጸሎት

      • “ልቤን መረመርክ” (3)

      • “በክንፎችህ ጥላ ሰውረኝ” (8)

  • 18

    • ዳዊት፣ አምላክ ስላዳነው ያቀረበው ውዳሴ

      • “ይሖዋ ቋጥኜ” ነው (2)

      • ይሖዋ ታማኝ ለሆነ ሰው ታማኝ ነው (25)

      • የአምላክ መንገድ ፍጹም ነው (30)

      • ‘ትሕትናህ ታላቅ ያደርገኛል’ (35)

  • 19

    • የአምላክ የፍጥረት ሥራና ሕግ ምሥክርነት ይሰጣሉ

      • “ሰማያት የአምላክን ክብር ይናገራሉ” (1)

      • የአምላክ ፍጹም ሕግ ኃይልን ያድሳል (7)

      • ‘ሳላውቅ የሠራኋቸው ኃጢአቶች’ (12)

  • 20

    • አምላክ የቀባውን ንጉሥ ያድናል

      • አንዳንዶች በሠረገሎችና በፈረሶች ይታመናሉ፤ ‘እኛ ግን የይሖዋን ስም እንጠራለን’ (7)

  • 21

    • በይሖዋ የሚታመነው ንጉሥ የሚያገኛቸው በረከቶች

      • ንጉሡ ረጅም ዕድሜ ተሰጠው (4)

      • የአምላክ ጠላቶች ድል ይደረጋሉ (8-12)

  • 22

    • ከተስፋ መቁረጥ ተላቆ ውዳሴ ማቅረብ

      • “አምላኬ ለምን ተውከኝ?” (1)

      • ‘በልብሴ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ’ (18)

      • በጉባኤ መካከል አምላክን ማወደስ (22, 25)

      • ምድር ሁሉ አምላክን ያመልካል (27)

  • 23

    • “ይሖዋ እረኛዬ ነው”

      • “የሚጎድልብኝ ነገር የለም” (1)

      • “ኃይሌን ያድሳል” (3)

      • “ጽዋዬ ጢም ብሎ ሞልቷል” (5)

  • 24

    • ክብር የተጎናጸፈው ንጉሥ

      • ‘ምድር የይሖዋ ናት’ (1)

  • 25

    • መመሪያና ምሕረት ለማግኘት የቀረበ ጸሎት

      • ‘ጎዳናህን አስተምረኝ’ (4)

      • “ከይሖዋ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት” መመሥረት (14)

      • ‘ኃጢአቴን ሁሉ ይቅር በል’ (18)

  • 26

    • ንጹሕ አቋም ይዞ መመላለስ

      • “ይሖዋ ሆይ፣ መርምረኝ” (2)

      • ከመጥፎ ጓደኞች መራቅ (4, 5)

      • ‘የአምላክን መሠዊያ እዞራለሁ’ (6)

  • 27

    • ይሖዋ የሕይወቴ ተገን ነው

      • የአምላክን ቤተ መቅደስ በአድናቆት መመልከት (4)

      • ‘አባቴና እናቴ ቢተዉኝ ይሖዋ ይቀበለኛል’ (10)

      • “ይሖዋን ተስፋ አድርግ” (14)

  • 28

    • የመዝሙራዊው ጸሎት ተሰሚነት አገኘ

      • ‘“ይሖዋ ብርታቴና ጋሻዬ ነው” (7)

  • 29

    • “የይሖዋ ድምፅ ኃይለኛ ነው”

      • ያጌጠ የቅድስና ልብስ ለብሳችሁ ይሖዋን አምልኩ (2)

      • “ክብር የተጎናጸፈው አምላክ አንጎደጎደ” (3)

      • “ይሖዋ ለሕዝቡ ብርታት ይሰጣል” (11)

  • 30

    • ሐዘን ወደ ደስታ ተለወጠ

      • ‘አምላክ ሞገስ የሚያሳየው ለዕድሜ ልክ ነው’ (5)

  • 31

    • ይሖዋን መጠጊያ ማድረግ

      • “መንፈሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ” (5)

      • ‘የእውነት አምላክ የሆነው ይሖዋ’ (5)

      • የአምላክ ጥሩነት ብዙ ነው (19)

  • 32

    • ይቅር የተባሉ ደስተኞች ናቸው

      • “ኃጢአቴን ለአንተ ተናዘዝኩ” (5)

      • አምላክ ጥልቅ ማስተዋል ይሰጥሃል (8)

  • 33

    • ለፈጣሪ የቀረበ ውዳሴ

      • “አዲስ መዝሙር ዘምሩለት” (3)

      • ይሖዋ በቃሉና በመንፈሱ የፈጠራቸው ነገ (6)

      • የይሖዋ ሕዝብ ደስተኛ ነው (12)

      • የይሖዋ ዓይኖች በትኩረት ይመለከታሉ (18)

  • 34

    • ይሖዋ አገልጋዮቹን ይታደጋል

      • “በኅብረት ስሙን ከፍ ከፍ እናድርግ” (3)

      • የይሖዋ መልአክ ይጠብቃል (7)

      • “ይሖዋ ጥሩ መሆኑን ቅመሱ፤ እዩም” (8)

      • ‘ከአጥንቶቹ አንዳቸውም አልተሰበሩም’ (20)

  • 35

    • ዳዊት፣ አምላክ ከጠላት እጅ እንዲታደገው ያቀረበው ጸሎት

      • ጠላቶች ይባረራሉ (5)

      • በብዙ ሕዝብ መካከል አምላክን ማወደስ (18)

      • ያለ ምክንያት ጠሉኝ (19)

  • 36

    • የአምላክ ታማኝ ፍቅር

      • ክፉ ሰው አምላክን አይፈራም (1)

      • አምላክ የሕይወት ምንጭ ነው (9)

      • “በብርሃንህ፣ ብርሃን ማየት እንችላለን” (9)

  • 37

    • በይሖዋ የሚታመኑ ይበለጽጋሉ

      • “በክፉዎች አትበሳጭ” (1)

      • “በይሖዋ ሐሴት አድርግ” (4)

      • “መንገድህን ለይሖዋ አደራ ስጥ” (5)

      • ‘የዋሆች ምድርን ይወርሳሉ’ (11)

      • ጻድቅ እህል ሲለምን አላየሁም (25)

      • ጻድቃን በምድር ላይ ለዘላለም ይኖራሉ (29)

  • 38

    • ንስሐ የገባ ሰው ያቀረበው ጸሎት

      • “በጭንቀት ተዋጥኩ፤ አንገቴንም ደፋሁ” (6)

      • ይሖዋ እሱን የሚጠባበቁ ሰዎችን ይሰማል (15)

      • ‘ኃጢአቴ አስጨንቆኝ ነበር’ (18)

  • 39

    • ሕይወት አጭር ነው

      • ሰው እንደ እስትንፋስ ነው (5, 11)

      • “እንባዬን ችላ አትበል” (12)

  • 40

    • ተወዳዳሪ ለማይገኝለት አምላክ የቀረበ ምስጋና

      • የአምላክን ሥራዎች ዘርዝረን መጨረስ አንችልም (5)

      • “መሥዋዕትንና መባን አልፈለግክም” (6)

      • “ፈቃድህን ማድረግ ያስደስተኛል” (8)

  • 41

    • የታመመ ሰው ጸሎት

      • አምላክ የታመመውን ይደግፈዋል (3)

      • የቅርብ ወዳጁ ከዳው (9)

  • 42

    • ታላቅ አዳኝ የሆነውን አምላክ ማወደስ

      • ርኤም ውኃ እንደምትጠማ አምላክን መጠማት (1, 2)

      • “ተስፋ የምቆርጠው ለምንድን ነው?” (5, 11)

      • “አምላክን በትዕግሥት እጠባበቃለሁ” (5, 11)

  • 43

    • ፈራጅ የሆነው አምላክ ይታደጋል

      • “ብርሃንህንና እውነትህን ላክ” (3)

      • “ተስፋ የምቆርጠው ለምንድን ነው?” (5)

      • “አምላክን በትዕግሥት እጠባበቃለሁ” (5)

  • 44

    • እርዳታ ለማግኘት የቀረበ ጸሎት

      • ‘ያዳንከን አንተ ነህ’ (7)

      • ‘እንደ እርድ በጎች ተቆጠርን’ (22)

      • “እኛን ለመርዳት ተነስ!” (26)

  • 45

    • የተቀባው ንጉሥ ጋብቻ

      • ጸጋ የተላበሱ ቃላት (2)

      • “አምላክ ለዘላለም ዙፋንህ ነው” (6)

      • ንጉሡ በሙሽራዋ ውበት ተማርኳል (11)

      • ወንዶች ልጆች በምድር ሁሉ ላይ መኳንንት ይሆናሉ (16)

  • 46

    • ‘አምላክ መጠጊያችን ነው’

      • የአምላክ አስደናቂ ሥራዎች (8)

      • አምላክ ጦርነትን ከመላው ምድር ላይ ያስወግዳል (9)

  • 47

    • አምላክ በመላው ምድር ላይ ነግሦአል

      • “ይሖዋ እጅግ የሚያስፈራ ነው” (2)

      • “ለአምላክ የውዳሴ መዝሙር ዘምሩ” (6, 7)

  • 48

    • ጽዮን፣ የታላቁ ንጉሥ ከተማ

      • “የምድር ሁሉ ደስታ” (2)

      • ከተማዋንና ማማዎቿን በሚገባ አጢኑ (11-13)

  • 49

    • በሀብት መታመን ሞኝነት ነው

      • ሌላውን መዋጀት የሚችል ሰው የለም (7, 8)

      • አምላክ ከመቃብር ይዋጃል (15)

      • ሀብት ከሞት ሊያድን አይችልም (16, 17)

  • 50

    • አምላክ በሕዝቡ ላይ ይፈርዳል

      • በመሥዋዕት አማካኝነት ከአምላክ ጋር የሚደረግ ቃል ኪዳን (5)

      • “አምላክ ራሱ ፈራጅ ነው” (6)

      • እንስሳት ሁሉ የአምላክ ናቸው (10, 11)

      • አምላክ ክፉዎችን ያጋልጣል (16-21)

  • 51

    • ንስሐ የገባ ሰው ጸሎት

      • ‘እናቴ በኃጢአት ፀነሰችኝ’ (5)

      • “ከኃጢአቴ አንጻኝ” (7)

      • “ንጹሕ ልብ ፍጠርልኝ” (10)

      • የተደቆሰ ልብ አምላክን ያስደስተዋል (17)

  • 52

    • በአምላክ ታማኝ ፍቅር መታመን

      • በክፋት የሚኩራሩ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው (1-5)

      • ፈሪሃ አምላክ የሌላቸው ሰዎች በሀብት ይታመናሉ (7)

  • 53

    • የሞኝ ሰው መገለጫ

      • “ይሖዋ የለም” (1)

      • “መልካም የሚሠራ ማንም የለም” (3)

  • 54

    • ዳዊት በጠላቶቹ መካከል ሳለ እርዳታ ለማግኘት ያቀረበው ጸሎት

      • “አምላክ ረዳቴ ነው” (4)

  • 55

    • ዳዊት፣ ወዳጁ በከዳው ጊዜ ያቀረበው ጸሎት

      • የቅርብ ወዳጁ ዘለፈው (12-14)

      • “ሸክምህን በይሖዋ ላይ ጣል” (22)

  • 56

    • ስደት በደረሰበት ጊዜ ያቀረበው ጸሎት

      • “በአምላክ እታመናለሁ” (4)

      • “እንባዬን በአቁማዳህ አጠራቅም” (8)

      • “ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?” (4, 11)

  • 57

    • ሞገስ ለማግኘት የቀረበ ልመና

      • በአምላክ ክንፎች ሥር መጠለል (1)

      • ጠላቶች በራሳቸው ወጥመድ ውስጥ ገቡ (6)

  • 58

    • በምድር ላይ የሚፈርድ አምላክ አለ

      • ክፉዎች እንዲቀጡ የቀረበ ጸሎት (6-8)

  • 59

    • አምላክ ጋሻና መጠጊያ ነው

      • ‘ለከሃዲዎች ምሕረት አታድርግ’ (5)

      • “ስለ ብርታትህ እዘምራለሁ” (16)

  • 60

    • አምላክ ጠላቶችን አሸነፈ

      • “የሰው ማዳን ከንቱ ነው” (11)

      • “አምላክ ኃይል ይሰጠናል” (12)

  • 61

    • አምላክ ከጠላት የሚጠብቅ ጽኑ ግንብ ነው

      • ‘በድንኳንህ በእንግድነት እቀመጣለሁ’ (4)

  • 62

    • እውነተኛ መዳን የሚገኘው ከአምላክ ነው

      • “ዝም ብዬ አምላክን እጠባበቃለሁ” (1, 5)

      • ‘ልባችሁን በአምላክ ፊት አፍስሱ’ (8)

      • ሰዎች እስትንፋስ ናቸው (9)

      • በሀብት አትታመኑ (10)

  • 63

    • አምላክን መናፈቅ

      • ‘ታማኝ ፍቅርህ ከሕይወት ይሻላል’ (3)

      • ‘ምርጥ የሆነውን በልቼ ጠገብኩ’ (5)

      • ሌሊት ስለ አምላክ ማሰላሰል (6)

      • ‘አምላክን የሙጥኝ እላለሁ’ (8)

  • 64

    • ስውር ከሆኑ ጥቃቶች ጥበቃ ማግኘት

      • “አምላክ ይመታቸዋል” (7)

  • 65

    • አምላክ ምድርን ይንከባከባል

      • “ጸሎት ሰሚ” (2)

      • ‘አንተ የመረጥከው ሰው ደስተኛ ነው’ (4)

      • የአምላክ ጥሩነት (11)

  • 66

    • አክብሮታዊ ፍርሃት የሚያሳድሩ የአምላክ ሥራዎች

      • “ኑና የአምላክን ሥራዎች ተመልከቱ” (5)

      • ‘ስእለቴን ለአንተ እፈጽማለሁ’ (13)

      • አምላክ ጸሎት ይሰማል (18-20)

  • 67

    • የምድር ዳርቻዎች አምላክን ይፈራሉ

      • የአምላክ መንገድ ይታወቃል (2)

      • “ሕዝቦች ሁሉ ያወድሱህ” (3, 5)

      • “አምላክ ይባርከናል” (6, 7)

  • 68

    • ‘የአምላክ ጠላቶች ይበታተኑ’

      • ‘አባት ለሌላቸው ልጆች አባት ነው’ (5)

      • አምላክ ብቸኛ ለሆነ ሰው ቤት ይሰጠዋል (6)

      • ምሥራቹን የሚያውጁ ሴቶች (11)

      • ሰዎችን እንደ ስጦታ አድርገህ ወሰድክ (18)

      • ‘ይሖዋ ሸክማችንን በየዕለቱ ይሸከማል’ (19)

  • 69

    • ጥበቃ ለማግኘት የቀረበ ጸሎት

      • “ለቤትህ ያለኝ ቅንዓት በልቶኛል” (9)

      • “በፍጥነት መልስልኝ” (17)

      • “ኮምጣጤ እንድጠጣ ሰጡኝ” (21)

  • 70

    • አፋጣኝ እርዳታ ለማግኘት የቀረበ ልመና

      • “ለእኔ ስትል ፈጥነህ እርምጃ ውሰድ” (5)

  • 71

    • በዕድሜ የገፉ ሰዎች ያላቸው የመተማመን ስሜት

      • ከልጅነት ጀምሮ በአምላክ መታመን (5)

      • ‘ጉልበቴ በሚያልቅበት ጊዜ አትተወኝ’ (9)

      • ‘አምላክ ከልጅነቴ ጀምሮ አስተምሮኛል’ (17)

  • 72

    • ሰላም የሰፈነበት የአምላክ ንጉሥ አገዛዝ

      • “ጻድቅ ይለመልማል” (7)

      • ከባሕር እስከ ባሕር ድረስ ተገዢዎች ይኖሩታል (8)

      • “ከግፍ ይታደጋቸዋል” (14)

      • “በምድር ላይ እህል ይትረፈረፋል” (16)

      • የአምላክ ስም ለዘላለም ይወደስ (19)

  • 73

    • ፈሪሃ አምላክ ያለው ሰው መንፈሳዊነቱን መልሶ አጠናከረ

      • “እግሮቼ ከመንገድ ሊወጡ ተቃርበው ነበር” (2)

      • ‘ቀኑን ሙሉ ተጨነቅኩ’ (14)

      • ‘ወደ አምላክ መቅደስ እስክገባ ድረስ’ (17)

      • ክፉዎች በሚያዳልጥ መሬት ላይ ናቸው (18)

      • “ወደ አምላክ መቅረብ ይበጀኛል” (28)

  • 74

    • አምላክ ሕዝቡን እንዲያስታውስ የቀረበ ጸሎት

      • አምላክ ያከናወናቸው የማዳን ሥራዎች (12-17)

      • ‘ጠላት እንደተሳለቀ አስብ’ (18)

  • 75

    • አምላክ በትክክል ይፈርዳል

      • ክፉዎች የይሖዋን ጽዋ ይጠጣሉ (8)

  • 76

    • አምላክ በጽዮን ጠላቶች ላይ የተቀዳጀው ድል

      • አምላክ የዋሆችን ያድናል (9)

      • ኩሩ የሆኑ ጠላቶች ይዋረዳሉ (12)

  • 77

    • በጭንቀት ጊዜ የቀረበ ጸሎት

      • በአምላክ ሥራዎች ላይ ማሰላሰል (11, 12)

      • “አምላክ ሆይ፣ እንደ አንተ ያለ ታላቅ አምላክ ማን ነው?” (13)

  • 78

    • የአምላክ እንክብካቤና የእስራኤላውያን እምነት ማጣት

      • ለመጪው ትውልድ ተናገሩ (2-8)

      • “በአምላክ ላይ እምነት አልጣሉም” (22)

      • ‘የሰማይ እህል’ (24)

      • ‘የእስራኤልን ቅዱስ እጅግ አሳዘኑት’ (41)

      • ከግብፅ አንስቶ እስከ ተስፋይቱ ምድር (43-55)

      • ‘አምላክን ተገዳደሩት’ (56)

  • 79

    • ብሔራት የአምላክን ሕዝብ በወረሩ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

      • “መሳለቂያ ሆንን” (4)

      • ‘ለስምህ ስትል እርዳን’ (9)

      • ‘ጎረቤቶቻችንን ሰባት እጥፍ አድርገህ ብድራታቸውን ክፈላቸው’ (12)

  • 80

    • የእስራኤል እረኛ ወደ ቀድሞው ሁኔታ እንዲመልሳቸው የቀረበ ልመና

      • “አምላክ ሆይ፣ ወደ ቀድሞው ሁኔታችን መልሰን” (3)

      • የአምላክ የወይን ተክል የሆነው እስራኤል (8-15)

  • 81

    • ታዛዥ እንዲሆኑ የቀረበ ማሳሰቢያ

      • ባዕዳን አማልክትን አታምልክ (9)

      • ‘ምነው ባዳመጥከኝ ኖሮ!’ (13)

  • 82

    • የጽድቅ ፍርድ ለማግኘት የቀረበ ልመና

      • አምላክ “በአማልክት” መካከል ይፈርዳል (1)

      • ‘ለችግረኛው ተሟገቱ’ (3)

      • “እናንተ አማልክት ናችሁ” (6)

  • 83

    • ከጠላት ጋር በተፋጠጡበት ጊዜ የቀረበ ጸሎት

      • “አምላክ ሆይ፣ ዝም አትበል” (1)

      • ጠላቶች ነፋስ እያሽከረከረ እንደሚወስደው ኮሸሽላ ናቸው (13)

      • የአምላክ ስም ይሖዋ ነው (18)

  • 84

    • የአምላክን ታላቅ የማደሪያ ድንኳን መናፈቅ

      • አንድ ሌዋዊ እንደ ወፍ ለመሆን ተመኘ (3)

      • “በቅጥር ግቢዎችህ አንዲት ቀን መዋል” (10)

      • “አምላክ ፀሐይና ጋሻ ነው” (11)

  • 85

    • ወደ ቀድሞው ሁኔታ እንዲመልሳቸው የቀረበ ጸሎት

      • አምላክ ለታማኝ አገልጋዮቹ ስለ ሰላም ይናገራል (8)

      • “ታማኝ ፍቅርና ታማኝነት ይገናኛሉ” (10)

  • 86

    • እንደ ይሖዋ ያለ አምላክ የለም

      • ይሖዋ ይቅር ለማለት ዝግጁ ነው (5)

      • ብሔራት ሁሉ አምላክን ያመልካሉ (9)

      • “መንገድህን አስተምረኝ” (11)

      • “ልቤን አንድ አድርግልኝ” (11)

  • 87

    • ጽዮን፣ የእውነተኛው አምላክ ከተማ

      • በጽዮን የተወለዱ (4-6)

  • 88

    • ከሞት ለመዳን የቀረበ ጸሎት

      • ‘ሕይወቴ በመቃብር አፋፍ ላይ ነች’ (3)

      • ‘በየማለዳው ወደ አንተ እጸልያለሁ’ (13)

  • 89

    • ስለ ይሖዋ ታማኝ ፍቅር መዘመር

      • ከዳዊት ጋር የተደረገ ቃል ኪዳን (3)

      • የዳዊት ዘር ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል (4)

      • አምላክ የቀባው ንጉሥ እሱን “አባቴ” ብሎ ይጠራዋል (26)

      • የዳዊት ቃል ኪዳን የጸና ነው (34-37)

      • ሰው ከመቃብር ሊያመልጥ አይችልም (48)

  • 90

    • የአምላክ ዘላለማዊነትና የሰው አጭር ዕድሜ

      • ሺህ ዓመት እንደ ትናንት ቀን ነው (4)

      • የሰው ዕድሜ ከ70-80 ዓመት ነው (10)

      • “ዕድሜያችንን እንዴት መቁጠር እንዳለብን አስተምረን” (12)

  • 91

    • በአምላክ ሚስጥራዊ ቦታ ጥበቃ ማግኘት

      • ከወፍ አዳኙ ወጥመድ መዳን (3)

      • በአምላክ ክንፎች ሥር መጠጊያ ማግኘት (4)

      • ‘በአጠገብህ ሺህ ቢወድቁም ወደ አንተ አይደርስም’ (7)

      • “መላእክቱን ስለ አንተ ያዛል” (11)

  • 92

    • ይሖዋ ለዘላለም ከፍ ከፍ ብሏል

      • ሥራው ታላቅ፣ ሐሳቡም ጥልቅ ነው (5)

      • ‘ጻድቅ እንደ ዛፍ ይለመልማል’ (12)

      • አረጋውያን ማበባቸውን ይቀጥላሉ (14)

  • 93

    • ግርማ የተላበሰው የይሖዋ አገዛዝ

      • “ይሖዋ ነገሠ!” (1)

      • ‘ማሳሰቢያዎችህ አስተማማኝ ናቸው’ (5)

  • 94

    • አምላክ የበቀል እርምጃ እንዲወስድ የቀረበ ጸሎት

      • “ክፉዎች እስከ መቼ ድረስ ይፈነጥዛሉ?” (3)

      • ያህ የሚሰጠው እርማት ደስታ ያስገኛል (12)

      • ‘አምላክ ሕዝቡን አይጥልም’ (14)

      • ‘በሕግ ስም ችግር መፍጠር’ (20)

  • 95

    • ታዛዥነት የታከለበት እውነተኛ አምልኮ

      • “ዛሬ ድምፁን የምትሰሙ ከሆነ” (7)

      • “ልባችሁን አታደንድኑ” (8)

      • “ወደ እረፍቴ አይገቡም” (11)

  • 96

    • “ለይሖዋ አዲስ መዝሙር ዘምሩ”

      • ይሖዋ እጅግ ሊወደስ ይገባዋል (4)

      • የሌሎች ሕዝቦች አማልክት ከንቱ ናቸው (5)

      • ያጌጠ የቅድስና ልብስ ለብሳችሁ ይሖዋን አምልኩ (9)

  • 97

    • ይሖዋ ከሌሎች አማልክት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ነው

      • “ይሖዋ ነገሠ!” (1)

      • ይሖዋን የምትወዱ፣ ክፋትን ጥሉ (10)

      • “ብርሃን ለጻድቃን ወጣ” (11)

  • 98

    • ይሖዋ፣ አዳኝና ጻድቅ ፈራጅ ነው

      • የይሖዋ ማዳን ታውቋል (2, 3)

  • 99

    • ቅዱስ ንጉሥ የሆነው ይሖዋ

      • ዙፋኑ ከኪሩቤል በላይ ነው (1)

      • ይቅር የሚልና የሚቀጣ አምላክ (8)

  • 100

    • ፈጣሪን ማመስገን

      • “ይሖዋን በደስታ አገልግሉት” (2)

      • ‘የሠራን አምላክ ነው’ (3)

  • 101

    • በንጹሕ አቋም የሚመላለስ ገዢ

      • ‘ትዕቢትን አልታገሥም’ (5)

      • ‘ወደ ታማኞች እመለከታለሁ’ (6)

  • 102

    • ጭቆና የደረሰበት ሰው ተስፋ በቆረጠ ጊዜ ያቀረበው ጸሎት

      • “በጣሪያ ላይ እንዳለች ብቸኛ ወፍ ሆንኩ” (7)

      • ‘የሕይወቴ ዘመን እንደሚጠፋ ጥላ ነው’ (11)

      • “ይሖዋ ጽዮንን ዳግመኛ ይገነባል” (16)

      • ይሖዋ ለዘላለም ይኖራል (26, 27)

  • 103

    • “ይሖዋን ላወድስ”

      • አምላክ በደላችንን ከእኛ አራቀ (12)

      • የአምላክ አባታዊ ምሕረት (13)

      • አምላክ አፈር መሆናችንን ያስታውሳል (14)

      • የይሖዋ ዙፋንና ንግሥና (19)

      • መላእክት የአምላክን ቃል ይፈጽማሉ (20)

  • 104

    • ድንቅ ለሆኑት የፍጥረት ሥራዎች አምላክን ማወደስ

      • ምድር ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች (5)

      • የወይን ጠጅና ምግብ ሰውን ያስደስታል (15)

      • “ሥራህ ምንኛ ብዙ ነው!” (24)

      • ‘መንፈሳቸውን ስትወስድ ይሞታሉ’ (29)

  • 105

    • ይሖዋ በታማኝነት ለሕዝቡ ያከናወናቸው ሥራዎች

      • አምላክ ቃል ኪዳኑን ያስታውሳል (8-10)

      • “የቀባኋቸውን አገልጋዮቼን አትንኩ” (15)

      • አምላክ ባሪያ በነበረው በዮሴፍ ተጠቀመ (17-22)

      • አምላክ በግብፅ ያከናወናቸው ተአምራት (23-36)

      • እስራኤል ከግብፅ ወጣ (37-39)

      • አምላክ ለአብርሃም የገባውን ቃል አስታወሰ (42)

  • 106

    • እስራኤል አድናቆት ሳያሳይ ቀረ

      • አምላክ ያደረገውን ነገር ወዲያውኑ ረሱ (13)

      • የአምላክን ክብር በኮርማ ምስል ለወጡ (19, 20)

      • ‘አምላክ በገባው ቃል ላይ እምነት አልነበራቸውም’ (24)

      • ‘ባአልን አመለኩ’ (28)

      • ልጆቻቸውን ለአጋንንት ሠዉ (37)

  • 107

    • አስደናቂ ለሆኑት ሥራዎቹ አምላክን አመስግኑ

      • “በትክክለኛው መንገድ መራቸው” (7)

      • የተጠማውንና የተራበውን አርክቷል (9)

      • ‘ከጨለማ አወጣቸው’ (14)

      • ቃሉን ልኮ ፈወሳቸው (20)

      • ‘ድሆችን ከጭቆና ይጠብቃል’ (41)

  • 108

    • በጠላት ላይ ድል ለመቀዳጀት የቀረበ ጸሎት

      • “የሰው ማዳን ከንቱ ነው” (12)

      • “አምላክ ኃይል ይሰጠናል” (13)

  • 109

    • የተጨነቀ ሰው ያቀረበው ጸሎት

      • “ሹመቱን ሌላ ሰው ይውሰደው” (8)

      • አምላክ በድሃው ቀኝ ይቆማል (31)

  • 110

    • እንደ መልከጼዴቅ ያለ ንጉሥና ካህን

      • ‘በጠላቶችህ መካከል ግዛ’ (2)

      • እንደ ጤዛ ያሉ ራሳቸውን በፈቃደኝነት የሚያቀርቡ ወጣቶች (3)

  • 111

    • ለታላላቅ ሥራዎቹ ይሖዋን አወድሱ

      • የአምላክ ስም ቅዱስና እጅግ የሚፈራ ነው (9)

      • ይሖዋን መፍራት ጥበብ ነው (10)

  • 112

    • ጻድቅ ሰው ይሖዋን ይፈራል

      • “በልግስና የሚያበድር ሰው ይሳካለታል” (5)

      • “ጻድቅ ለዘላለም ሲታወስ ይኖራል” (6)

      • ለጋስ ለድሆች ይሰጣል (9)

  • 113

    • ከፍ ባለ ቦታ ያለው አምላክ ችግረኛውን ያነሳል

      • የይሖዋ ስም ለዘላለም ይወደስ (2)

      • አምላክ ወደ ታች ያጎነብሳል (6)

  • 114

    • እስራኤል ከግብፅ ወጣ

      • ባሕሩ ሸሸ (5)

      • ተራሮች እንደ አውራ በግ ዘለሉ (6)

      • ጠንካራውን ዓለት ወደ ውኃ ምንጮች ይለውጣል (8)

  • 115

    • ክብር መሰጠት ያለበት ለአምላክ ብቻ ነው

      • በድን የሆኑ ጣዖታት (4-8)

      • ምድር ለሰው ልጆች ተሰጠች (16)

      • ‘ሙታን ያህን አያወድሱም’ (17)

  • 116

    • የምስጋና መዝሙር

      • “ለይሖዋ ምን እመልስለታለሁ?” (12)

      • “የማዳንን ጽዋ አነሳለሁ” (13)

      • “ስእለቴን ለይሖዋ እፈጽማለሁ” (14, 18)

      • የአገልጋዮቹ ሞት በይሖዋ ዓይን ከባድ ነገር ነው (15)

  • 117

    • ብሔራት ሁሉ ይሖዋን እንዲያወድሱ የቀረበ ጥሪ

      • የአምላክ ታማኝ ፍቅር ታላቅ ነው (2)

  • 118

    • ይሖዋ ላስገኘው ድል ምስጋና ማቅረብ

      • ‘ያህን ተጣራሁ፤ እሱም መለሰልኝ’ (5)

      • “ይሖዋ ከጎኔ ነው” (6, 7)

      • የተናቀው ድንጋይ የማዕዘን ራስ ድንጋይ ይሆናል (22)

      • “በይሖዋ ስም የሚመጣው” (26)

  • 119

    • ውድ ለሆነው የአምላክ ቃል አድናቆት ማሳየት

      • “ወጣቶች በንጽሕና መመላለስ የሚችሉት እንዴት ነው?” (9)

      • “ማሳሰቢያዎችህን እወዳቸዋለሁ” (24)

      • “ቃልህ ተስፋዬ ነው” (74, 81, 114)

      • “ሕግህን ምንኛ ወደድኩ!” (97)

      • “ከአስተማሪዎቼ ሁሉ የበለጠ ጥልቅ ማስተዋል አለኝ” (99)

      • ‘ቃልህ ለእግሬ መብራት ነው’ (105)

      • “የቃልህ ፍሬ ነገር እውነት ነው” (160)

      • የአምላክን ሕግ የሚወዱ ሰላም አላቸው (165)

  • 120

    • ሰላምን የናፈቀ የባዕድ አገር ሰው

      • “ከአታላይ አንደበት ታደገኝ” (2)

      • “እኔ ለሰላም ቆሜአለሁ” (7)

  • 121

    • ይሖዋ ሕዝቡን ይጠብቃል

      • ‘እርዳታ የማገኘው ከይሖዋ ነው’ (2)

      • ይሖዋ ፈጽሞ አያንቀላፋም (3, 4)

  • 122

    • ለኢየሩሳሌም ሰላም የቀረበ ጸሎት

      • ወደ ይሖዋ ቤት መሄድ የሚያስገኘው ደስታ (1)

      • አንድ ወጥ ሆና የተገነባች ከተማ (3)

  • 123

    • የይሖዋን ሞገስ መሻት

      • ‘ወደ ይሖዋ እንመለከታለን’ (2)

      • “ንቀት እጅግ በዝቶብናል” (3)

  • 124

    • “ይሖዋ ከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ”

      • ከተሰበረ ወጥመድ ማምለጥ (7)

      • “የይሖዋ ስም ረዳታችን ነው” (8)

  • 125

    • ይሖዋ ሕዝቡን ይጠብቃል

      • “ተራሮች በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንዳሉ ሁሉ” (2)

      • “በእስራኤል ሰላም ይስፈን” (5)

  • 126

    • ጽዮን ወደ ቀድሞ ሁኔታዋ ተመለሰች

      • “ይሖዋ ታላላቅ ነገሮች አደረገልን” (3)

      • ለቅሷቸው ወደ ደስታ ይለወጣል (5, 6)

  • 127

    • ያለ አምላክ እርዳታ ሁሉ ነገር ከንቱ ድካም ነው

      • “ይሖዋ ቤትን ካልሠራ” (1)

      • ልጆች ከይሖዋ የተገኙ ስጦታዎች ናቸው (3)

  • 128

    • ይሖዋን በመፍራት የሚገኝ ደስታ

      • እንደሚያፈራ ወይን የሆነች ሚስት (3)

      • “የኢየሩሳሌምን ብልጽግና ለማየት ያብቃህ” (5)

  • 129

    • አጠቁኝ፤ ሊያሸንፉኝ ግን አልቻሉም

      • ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ ኀፍረት ይከናነባሉ (5)

  • 130

    • “ከጥልቅ ውስጥ አንተን እጣራለሁ”

      • “አንተ ስህተትን የምትከታተል ቢሆን ኖሮ” (3)

      • በይሖዋ ዘንድ ይቅርታ አለ (4)

      • “ይሖዋን በጉጉት እጠባበቃለሁ” (6)

  • 131

    • “ጡት እንደጣለ ሕፃን ረካሁ”

      • ‘ታላላቅ ነገሮችን አልመኝም’ (1)

  • 132

    • ዳዊትና ጽዮን ተመረጡ

      • “የቀባኸውን ሰው ገሸሽ አታድርግ” (10)

      • ካህናቷ መዳንን ይለብሳሉ (16)

  • 133

    • በአንድነት አብሮ መኖር

      • በአሮን ራስ ላይ እንደፈሰሰ ዘይት (2)

      • እንደ ሄርሞን ጤዛ (3)

  • 134

    • በሌሊት አምላክን ማወደስ

      • “እጆቻችሁን በቅድስና ወደ ላይ አንሱ” (2)

  • 135

    • ለታላቅነቱ ያህን አወድሱ

      • ‘በግብፅ ምልክቶችንና ተአምራትን አደረገ’ (8, 9)

      • “ስምህ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል” (13)

      • በድን የሆኑ ጣዖታት (15-18)

  • 136

    • የይሖዋ ታማኝ ፍቅር ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል

      • ሰማይንና ምድርን በጥበብ ሠራ (5, 6)

      • ፈርዖን ቀይ ባሕር ውስጥ ሞተ (15)

      • አምላክ የተጨነቁትን ያስታውሳል (23)

      • “ሕይወት ላለው ሁሉ ምግብ ይሰጣል” (25)

  • 137

    • በባቢሎን ወንዞች አጠገብ

      • የጽዮንን መዝሙሮች አልዘመሩም (3, 4)

      • ባቢሎን ትጠፋለች (8)

  • 138

    • አምላክ ከፍ ያለ ቢሆንም ያስብልናል

      • ‘ጸሎቴን መለስክልኝ’ (3)

      • ‘በአደጋ መካከል እንኳ ሕይወቴን ትጠብቃለህ’ (7)

  • 139

    • አምላክ አገልጋዮቹን በሚገባ ያውቃል

      • ከአምላክ መንፈስ ማምለጥ አይቻልም (7)

      • ‘ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁ’ (14)

      • ‘ፅንስ እያለሁ ዓይኖችህ አዩኝ’ (16)

      • ‘በዘላለም መንገድ ምራኝ’ (24)

  • 140

    • ኃያል አዳኝ የሆነው ይሖዋ

      • ክፉዎች እንደ እባብ ናቸው (3)

      • ጨካኞች ጥፋት ይደርስባቸዋል (11)

  • 141

    • ጥበቃ ለማግኘት የቀረበ ጸሎት

      • ‘ጸሎቴ እንደ ዕጣን ይሁን’ (2)

      • የጻድቅ ወቀሳ እንደ ዘይት ነው (5)

      • ‘ክፉዎች የገዛ ወጥመዳቸው ውስጥ ይወድቃሉ’ (10)

  • 142

    • ከአሳዳጆቹ እንዲታደገው ያቀረበው ጸሎት

      • “ሸሽቼ ማምለጥ የምችልበት ቦታ የለም” (4)

      • “ያለኸኝ አንተ ብቻ ነህ” (5)

  • 143

    • ‘እንደ ደረቅ ምድር አምላክን ተጠማሁ’

      • ‘የእጆችህን ሥራ አውጠነጥናለሁ’ (5)

      • “ፈቃድህን እንድፈጽም አስተምረኝ” (10)

      • ‘መንፈስህ ይምራኝ’ (10)

  • 144

    • ድል ለመቀዳጀት የቀረበ ጸሎት

      • “ሟች የሆነው የሰው ልጅ ምንድን ነው?” (3)

      • ‘ጠላቶች ይበተኑ’ (6)

      • የይሖዋ ሕዝብ ደስተኛ ነው (15)

  • 145

    • ታላቅ ንጉሥ የሆነውን አምላክ ማወደስ

      • ‘የአምላክን ታላቅነት አውጃለሁ’ (6)

      • “ይሖዋ ለሁሉም ጥሩ ነው” (9)

      • ‘ታማኝ አገልጋዮችህ ያወድሱሃል’ (10)

      • የአምላክ ዘላለማዊ ንግሥና (13)

      • ‘የሕያዋን ፍጥረታትን ሁሉ ፍላጎት ታሟላለህ’ (16)

  • 146

    • በሰው ሳይሆን በአምላክ መታመን

      • ሰው ሲሞት ሐሳቡ ሁሉ ይጠፋል (4)

      • አምላክ ያጎነበሱትን ቀና ያደርጋል (8)

  • 147

    • አምላክን ድንቅ ለሆኑት ሥራዎቹ ማወደስ

      • የተሰበረ ልብ ያላቸውን ይፈውሳል (3)

      • ከዋክብትን ሁሉ በስማቸው ይጠራቸዋል (4)

      • በረዶን እንደ ሱፍ ይልካል (16)

  • 148

    • ፍጥረት ሁሉ ይሖዋን ያወድስ

      • “መላእክቱ ሁሉ፣ አወድሱት” (2)

      • ‘ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብት አወድሱት’ (3)

      • ወጣቶችና ሽማግሌዎች አምላክን አወድሱ (12, 13)

  • 149

    • አምላክን ለተቀዳጀው ድል በመዝሙር ማወደስ

      • አምላክ በሕዝቡ ደስ ይሰኛል (4)

      • የአምላክ ታማኝ አገልጋዮች ክብር ይገባቸዋል (9)

  • 150

    • እስትንፋስ ያለው ሁሉ ያህን ያወድስ

      • ሃሌሉያህ! (1, 6)