በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ጥያቄ 13

መጽሐፍ ቅዱስ ሥራን አስመልክቶ ምን ይላል?

 “በሥራው የተካነን ሰው አይተሃል? በነገሥታት ፊት ይቆማል፤ ተራ በሆኑ ሰዎች ፊት አይቆምም።”

ምሳሌ 22:29

 “የሚሰርቅ ከእንግዲህ ወዲህ አይስረቅ፤ ከዚህ ይልቅ ለተቸገረ ሰው የሚያካፍለው ነገር እንዲኖረው በእጆቹ መልካም ተግባር እያከናወነ በትጋት ይሥራ።”

ኤፌሶን 4:28

 “ለሰው ከመብላትና ከመጠጣት እንዲሁም ተግቶ በሚሠራው ሥራ ሁሉ ደስታ ከማግኘት የተሻለ ነገር የለም። ይህ የአምላክ ስጦታ ነው።”

መክብብ 3:13