ኢሳይያስ 11:1-16

  • የእሴይ ቀንበጥ የጽድቅ አገዛዝ (1-10)

    • ተኩላ ከበግ ጠቦት ጋር ይቀመጣል (6)

    • ምድር በይሖዋ እውቀት ትሞላለች (9)

  • የሕዝቡ ቀሪዎች ይመለሳሉ (11-16)

11  ከእሴይ+ ጉቶ፣ ቅርንጫፍ ይወጣል፤ከሥሮቹም የሚወጣው ቀንበጥ ፍሬ ያፈራል።+   በእሱም ላይ የይሖዋ መንፈስ፣+የጥበብና+ የማስተዋል መንፈስ፣የምክርና የኃይል+ መንፈስ፣የእውቀትና ይሖዋን የመፍራት መንፈስ ያርፍበታል።   ይሖዋን በመፍራትም ደስ ይሰኛል።+ ዓይኑ እንዳየ አይፈርድምወይም ጆሮው በሰማው ነገር ላይ ብቻ ተመሥርቶ አይወቅስም።+   ለችግረኞች በትክክል* ይፈርዳል፤በምድር ላሉ የዋሆች ጥቅም ሲል ሌሎችን ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ይወቅሳል። በአፉም በትር ምድርን ይመታል፤+በከንፈሩም እስትንፋስ* ክፉዎችን ይገድላል።+   ጽድቅ የወገቡ መታጠቂያ፣ታማኝነትም የጎኑ መታጠቂያ ይሆናል።+   ተኩላ ከበግ ጠቦት ጋር የሚቀመጥበት ጊዜ ይኖራል፤+ነብርም ከፍየል ግልገል ጋር ይተኛል፤ጥጃ፣ አንበሳና* የሰባ ከብት አብረው ይሆናሉ፤*+ትንሽ ልጅም ይመራቸዋል።   ላምና ድብ አብረው ይበላሉ፤ልጆቻቸውም አብረው ይተኛሉ። አንበሳ እንደ በሬ ገለባ ይበላል።+   ጡት የሚጠባ ሕፃንም በእባብ* ጉድጓድ ላይ ይጫወታል፤ጡት የጣለውም ሕፃን እጁን በመርዘኛ እባብ ጎሬ ላይ ያደርጋል።   በተቀደሰው ተራራዬ ሁሉ ላይምንም ዓይነት ጉዳት ወይም ጥፋት አያደርሱም፤+ምክንያቱም ውኃ ባሕርን እንደሚሸፍንምድርም በይሖዋ እውቀት ትሞላለች።+ 10  በዚያን ቀን የእሴይ ሥር+ ለሕዝቦች ምልክት* ሆኖ ይቆማል።+ ብሔራት ከእሱ መመሪያ ይሻሉ፤*+ማረፊያ ስፍራውም እጅግ የከበረ ይሆናል። 11  በዚያን ቀን ይሖዋ ዳግመኛ እጁን ዘርግቶ የተረፉትን የሕዝቡን ቀሪዎች ለሁለተኛ ጊዜ ከአሦር፣+ ከግብፅ፣+ ከጳትሮስ፣+ ከኢትዮጵያ፣*+ ከኤላም፣+ ከሰናኦር፣* ከሃማትና ከባሕር ደሴቶች+ መልሶ ይሰበስባል። 12  ለብሔራት ምልክት* ያቆማል፤ በየቦታው የተሰራጩትን እስራኤላውያንም መልሶ ያመጣቸዋል፤+ እንዲሁም የተበታተኑትን የይሁዳ ሰዎች ከአራቱም የምድር ማዕዘኖች ይሰበስባል።+ 13  የኤፍሬም ቅናት ይወገዳል፤+ይሁዳንም የሚጠሉ ይጠፋሉ። ኤፍሬም በይሁዳ አይቀናም፤ይሁዳም ኤፍሬምን አይጠላውም።+ 14  በምዕራብ በኩል በፍልስጤም ተረተር* ላይ በድንገት ይወርዳሉ፤ግንባር ፈጥረው በምሥራቅ የሚኖሩ ሕዝቦችን ይዘርፋሉ። በኤዶምና+ በሞዓብ+ ላይ እጃቸውን* ይዘረጋሉ፤አሞናውያንም ተገዢዎቻቸው ይሆናሉ።+ 15  ይሖዋ የግብፅን ባሕረ ሰላጤ* ይከፍላል፤*+በወንዙም*+ ላይ እጁን በዛቻ ያወዛውዛል። በሚያቃጥል እስትንፋሱ* የወንዙን ሰባት ጅረቶች ይመታል፤*ሰዎችም ከነጫማቸው እንዲሻገሩ ያደርጋል። 16  እስራኤል ከግብፅ ምድር በወጣበት ጊዜ እንደሆነው ሁሉ፣ከሕዝቡ የተረፉት ቀሪዎችም+ ከአሦር የሚወጡበት ጎዳና+ ይኖራል።

የግርጌ ማስታወሻዎች

ወይም “በጽድቅ።”
ወይም “መንፈስ።”
ወይም “ደቦል አንበሳና።”
“ጥጃና አንበሳ አብረው ይሰማራሉ” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ወይም “በጉበና።” በእስያና በአፍሪካ የሚገኝ እጅግ መርዘኛ የሆነ እባብ፤ ኮብራ።
ወይም “ለምልክት የሚተከል ምሰሶ።”
ወይም “ብሔራት እሱን ይፈልጉታል።”
ባቢሎንን ያመለክታል።
ወይም “ከኩሽ።”
ወይም “ለምልክት የሚተከል ምሰሶ።”
ወይም “ኃይላቸውን።”
ቃል በቃል “ትከሻ።”
ቃል በቃል “ምላስ።”
“ያደርቃል” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ኤፍራጥስን ያመለክታል።
ወይም “መንፈሱ።”
“ወንዙን መትቶ ሰባት ጅረት ያደርገዋል” ማለትም ሊሆን ይችላል።