በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የመክብብ መጽሐፍ

ምዕራፎች

1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12

የመጽሐፉ ይዘት

  • 1

    • “ሁሉም ነገር ከንቱ ነው!” (1-11)

      • ‘ምድር ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች’ (4)

      • የተፈጥሮ ዑደቶች ቀጣይ ናቸው (5-7)

      • “ከፀሐይ በታች ምንም አዲስ ነገር የለም” (9)

    • የሰው ጥበብ ውስን ነው (12-18)

      • ነፋስን ማሳደድ (14)

  • 2

    • ሰለሞን፣ ያከናወናቸውን ሥራዎች መለስ ብሎ አሰበ (1-11)

    • የሰው ጥበብ ያለው አንጻራዊ ጥቅም (12-16)

    • የሰው ልፋት ከንቱ ነው (17-23)

    • ብላ፣ ጠጣ እንዲሁም በሥራህ ተደሰት (24-26)

  • 3

    • “ለሁሉም ነገር ጊዜ አለው” (1-8)

    • በሕይወት መደሰት የአምላክ ስጦታ ነው (9-15)

      • ዘላለማዊነትን በሰው ልብ ውስጥ አኑሯል (11)

    • አምላክ በፍትሕ ይፈርዳል (16, 17)

    • ሰዎችም ሆኑ እንስሳት፣ ሁሉም ይሞታሉ (18-22)

      • “ሁሉም ወደ አፈር ይመለሳሉ” (20)

  • 4

    • ግፍ ከሞት የከፋ ነው (1-3)

    • ለሥራ ሚዛናዊ አመለካከት መያዝ (4-6)

    • የጓደኛ ጥቅም (7-12)

      • “አንድ ከመሆን ሁለት መሆን ይሻላል” (9)

    • የንጉሥ ሕይወት ከንቱ ሊሆን ይችላል (13-16)

  • 5

    • ለአምላክ ተገቢውን ፍርሃት ማሳየት (1-7)

    • ከፍተኛ ቦታ ያላቸው ከእነሱ በታች ያሉትን ይመለከታሉ (8, 9)

    • የሀብት ከንቱነት (10-20)

      • ገንዘብን የሚወዱ አይጠግቡም (10)

      • “የሠራተኛ እንቅልፍ ጣፋጭ ነው” (12)

  • 6

    • ሰው ባፈራው ንብረት ላይደሰት ይችላል (1-6)

    • ባለህ ነገር ተደሰት (7-12)

  • 7

    • ጥሩ ስምና የሞት ቀን (1-4)

    • የጥበበኛ ሰው ወቀሳ (5-7)

    • “የአንድ ነገር ፍጻሜ ከጅማሬው ይሻላል” (8-10)

    • ጥበብ የሚያስገኘው ጥቅም (11, 12)

    • ጥሩ ቀንና መጥፎ ቀን (13-15)

    • ከልኩ አትለፍ (16-22)

    • ሰብሳቢው ያስተዋላቸው ነገሮች (23-29)

  • 8

    • ፍጽምና የጎደለው የሰው አገዛዝ (1-17)

      • “የንጉሥን ትእዛዝ አክብር” (2-4)

      • “ሰው ሰውን የገዛው ለጉዳቱ ነው” (9)

      • አፋጣኝ ፍርድ ሳይሰጥ ሲቀር (11)

      • ብላ፣ ጠጣ ደግሞም ተደሰት (15)

  • 9

    • “ፍጻሜያቸው ተመሳሳይ ነው” (1-3)

    • ከመሞትህ በፊት በሕይወትህ ተደሰት (4-12)

      • ‘ሙታን ምንም አያውቁም’ (5)

      • በመቃብር ምንም ሥራ የለም (10)

      • “ጊዜና ያልተጠበቁ ክስተቶች” (11)

    • ጥበብ የሚናቅበት ጊዜ አለ (13-18)

  • 10

    • ትንሽ ሞኝነት ጥበብን ዋጋ ያሳጣል (1)

    • የችሎታ ማነስ አደጋ ላይ ይጥላል (2-11)

    • ሞኝ ሰው የሚደርስበት አሳዛኝ መከራ (12-15)

    • የገዢዎች ሞኝነት (16-20)

      • ቃልህን ወፍ ደግማ ልትናገር ትችላለች (20)

  • 11

    • በተከፈተልህ አጋጣሚ ተጠቀም (1-8)

      • “ቂጣህን በውኃ ላይ ጣል” (1)

      • ከማለዳ እስከ ምሽት ዘርህን ዝራ (6)

    • የወጣትነት ዕድሜህን በማስተዋል ተጠቀምበት (9, 10)

  • 12

    • እርጅና ሳይመጣ ፈጣሪን አስብ (1-8)

    • የሰብሳቢው የመደምደሚያ ቃላት (9-14)

      • “የጥበበኞች ቃላት እንደ በሬ መውጊያ ናቸው” (11)

      • “እውነተኛውን አምላክ ፍራ” (13)