በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 25

የስብሰባ አዳራሾችን የምንሠራው ለምንድን ነው? የሚገነቡትስ እንዴት ነው?

የስብሰባ አዳራሾችን የምንሠራው ለምንድን ነው? የሚገነቡትስ እንዴት ነው?

ቦሊቪያ

ናይጄሪያ፣ በፊትና አሁን

ታሂቲ

በስብሰባ አዳራሽ ውስጥ የሚሰጠው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት የሚያጠነጥነው የኢየሱስ አገልግሎት ዋነኛ ጭብጥ በነበረው በአምላክ መንግሥት ዙሪያ ነው።—ሉቃስ 8:1

በማኅበረሰቡ ውስጥ የእውነተኛ አምልኮ ማዕከል ናቸው። የመንግሥቱን ምሥራች የመስበኩ ሥራ የሚደራጀው በእነዚህ የስብሰባ አዳራሾች ነው። (ማቴዎስ 24:14) የስብሰባ አዳራሾች መጠናቸውም ሆነ አሠራራቸው ይለያይ እንጂ ሁሉም ልከኛ የሆኑ የመሰብሰቢያ ቦታዎች ናቸው፤ በአብዛኛው በአንድ አዳራሽ ውስጥ ከአንድ የሚበልጡ ጉባኤዎች ይሰበሰባሉ። በቅርብ ዓመታት ውስጥ የጉባኤዎቻችን ቁጥር በጣም በመጨመሩ በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ (በአማካይ በየቀኑ አምስት) አዳዲስ የስብሰባ አዳራሾችን ገንብተናል። ይህ ሊሆን የቻለው እንዴት ነው?—ማቴዎስ 19:26

አዳራሾቹ የሚገነቡት ለዚህ ዓላማ በሚደረጉ መዋጮዎች ነው። እነዚህ መዋጮዎች ወደ ቅርንጫፍ ቢሮው የሚላኩ ሲሆን የስብሰባ አዳራሽ መገንባት ወይም ማደስ የሚያስፈልጋቸው ጉባኤዎች በዚህ ገንዘብ መጠቀም ይችላሉ።

አዳራሾቹን የሚገነቡት ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ደሞዝ የማይከፈላቸው ፈቃደኛ ሠራተኞች ናቸው። በብዙ አገሮች የስብሰባ አዳራሽ ግንባታ ቡድኖች አሉ። የግንባታ አገልጋዮችና ሌሎች ፈቃደኛ ሠራተኞች የሚገኙባቸው ቡድኖች በአንድ አገር ውስጥ ከጉባኤ ወደ ጉባኤ አልፎ ተርፎም በጣም ሩቅ ወደሆኑ አካባቢዎች እየሄዱ ጉባኤዎች የራሳቸውን የስብሰባ አዳራሽ መገንባት እንዲችሉ እገዛ ያበረክታሉ። በሌሎች አገሮች ደግሞ ብቃት ያላቸው የይሖዋ ምሥክሮች በተመደበላቸው አካባቢ ውስጥ የሚከናወኑትን የስብሰባ አዳራሽ ግንባታና እድሳት ሥራዎች እንዲከታተሉ ይሾማሉ። በፈቃደኝነት በሥራው የሚካፈሉ ችሎታ ያላቸው በርካታ ባለሙያዎች ቢኖሩም እንኳ በእያንዳንዱ የግንባታ ቦታ አብዛኛውን የግንባታ ሥራ የሚያከናውኑት የጉባኤው አባላት ናቸው። ይህ ሁሉ ሥራ መከናወን የቻለው በይሖዋ መንፈስ ድጋፍና የአምላክ ሕዝቦች በሙሉ ነፍሳቸው በሚያደርጉት እገዛ ነው።—መዝሙር 127:1፤ ቆላስይስ 3:23

  • የስብሰባ አዳራሾችን የምንገነባው ለምንድን ነው?

  • በመላው ዓለም የስብሰባ አዳራሾችን መገንባት የተቻለው እንዴት ነው?