ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በተለያዩ ዘመናት የተከናወኑ ነገሮችን እንመለከታለን፤ ከእነዚህም መካከል ስለ ፍጥረት የሚናገረው ዘገባ፣ ስለ ኢየሱስ መወለድና ስላከናወነው አገልግሎት የሚገልጸው ታሪክ እንዲሁም የአምላክ መንግሥት ስለሚያመጣቸው በረከቶች የሚናገረው ዘገባ ይገኙበታል።
የበላይ አካሉ መልእክት
ይህን መጽሐፍ እንዴት ልንጠቀምበት እንችላለን?
ትምህርት 1
አምላክ ሰማይንና ምድርን ሠራ
መጽሐፍ ቅዱስ አምላክ ሰማይንና ምድርን እንደፈጠረ ይናገራል። አምላክ ሌሎች ነገሮችን ሁሉ ከመፍጠሩ በፊት አንድ መልአክ የፈጠረው ለምንድን ነው?
ትምህርት 2
አምላክ የመጀመሪያዎቹን ወንድና ሴት ፈጠረ
አምላክ የመጀመሪያዎቹን ወንድና ሴት ከፈጠረ በኋላ በኤደን የአትክልት ስፍራ አስቀመጣቸው። ቤተሰብ መሥርተው መላዋን ምድር ገነት እንዲያደርጉ ፈልጎ ነበር።
ትምህርት 3
አዳምና ሔዋን አምላክን ሳይታዘዙ ቀሩ
በኤደን የአትክልት ስፍራ ውስጥ የነበረው አንድ ዛፍ ከሌሎቹ የተለየ ነበር የምንለው ለምንድን ነው? ሔዋን የዚህን ዛፍ ፍሬ የበላችው ለምንድን ነው?
ትምህርት 4
ቃየን ተናዶ ወንድሙን ገደለው
አምላክ የአቤልን መባ ሲቀበል የቃየንን ግን አልተቀበለም። ቃየን ይህን ሲያውቅ በጣም ስለተናደደ መጥፎ ነገር አደረገ።
ትምህርት 5
የኖኅ መርከብ
ክፉ መላእክት በምድር ላይ የሚኖሩ ሴቶችን አግብተው ግዙፍና ጉልበተኛ የሆኑ ልጆችን ወለዱ። በሁሉም ቦታ ዓመፅ ተስፋፍቶ ነበር። ኖኅ ግን ከሌሎቹ የተለየ ነበር፤ አምላክን ይወድና ይታዘዝ ነበር።
ትምህርት 6
ስምንት ሰዎች ከጥፋት ውኃው ተረፉ
አምላክ በኖኅ ዘመን የነበረውን ዓለም ለማጥፋት 40 ቀንና 40 ሌሊት እንዲዘንብ አደረገ። ኖኅና ቤተሰቡ ከአንድ ዓመት በላይ በመርከቡ ውስጥ ቆዩ። በመጨረሻም መውጣት ቻሉ።
ትምህርት 7
የባቤል ግንብ
አንዳንድ ሰዎች ከተማ ለመገንባትና ሰማይ የሚደርስ ግንብ ለመሥራት አስበው ነበር። ይሖዋ የተለያየ ቋንቋ እንዲናገሩ ያደረጋቸው ለምንድን ነው?
ትምህርት 8
አብርሃምና ሣራ አምላክን ታዘዋል
አብርሃምና ሣራ በዑር ከተማ የነበራቸውን ሕይወት ትተው በከነአን ምድር ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ ለመኖር ፈቃደኛ የሆኑት ለምንድን ነው?
ትምህርት 10
የሎጥን ሚስት አስታውሱ
አምላክ በሰዶምና በገሞራ ላይ እሳትና ድኝ አዘነበ። እነዚህ ከተሞች የጠፉት ለምንድን ነው? የሎጥን ሚስት ማስታወስ ያለብን ለምንድን ነው?
ትምህርት 11
የአብርሃም እምነት ተፈተነ
አምላክ አብርሃምን ‘እባክህ አንድ ልጅህን ወስደህ በሞሪያ ምድር በሚገኝ ተራራ ላይ መሥዋዕት አድርገህ አቅርበው’ አለው። አብርሃም ይህን የእምነት ፈተና እንዴት ይወጣው ይሆን?
ትምህርት 12
ያዕቆብ ውርስ አገኘ
ይስሐቅና ርብቃ፣ ኤሳውና ያዕቆብ የሚባሉ መንታ ልጆች ነበሯቸው። መጀመሪያ የተወለደው ኤሳው ስለነበር ለየት ያለ ውርስ የሚያገኘው እሱ ነበር። ለአንድ ሳህን ወጥ ሲል ይህን ውርስ አሳልፎ የሰጠው ለምንድን ነው?
ትምህርት 19
የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች
ትዕቢተኛ የነበረው ፈርዖን አምላክ ያዘዘውን ቀላል ነገር ለመፈጸም ፈቃደኛ ባለመሆኑ በሕዝቡ ላይ መከራ እንዲመጣ አድርጓል።
ትምህርት 32
አዲሱ መሪና ሁለቱ ደፋር ሴቶች
ኢያሱ ከሞተ በኋላ እስራኤላውያን ጣዖት ማምለክ ጀመሩ። በዚህ የተነሳ ችግር ገጥሟቸው የነበረ ቢሆንም በመስፍኑ ባርቅ፣ በነቢይቱ ዲቦራና በኢያዔል አማካኝነት እርዳታ አገኙ።
ትምህርት 33
ሩትና ናኦሚ
ባሎቻቸው የሞቱባቸው ሁለት ሴቶች ወደ እስራኤል ተመለሱ። አንደኛዋ ሴት ማለትም ሩት በእርሻ ላይ ለመሥራት ስትሄድ ቦዔዝ ተመለከታት።
ትምህርት 34
ጌድዮን ምድያማውያንን አሸነፈ
እስራኤላውያን፣ ምድያማውያን ሲያሠቃዩአቸው እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ጮኹ። የጌድዮን ጥቂት ወታደሮች 135,000ዎቹን የጠላት ወታደሮች ያሸነፉት እንዴት ነው?
ትምህርት 35
ሐና ልጅ ለማግኘት ጸለየች
ሕልቃና ሐናን፣ ፍናናንና ልጆቹን ይዞ በሴሎ በሚገኘው የማደሪያ ድንኳን ይሖዋን ለማምለክ ሄደ። በዚያም ሐና ልጅ ለማግኘት ጸለየች። በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሳሙኤልን ወለደች!
ትምህርት 37
ይሖዋ ሳሙኤልን አነጋገረው
የሊቀ ካህናቱ የኤሊ ሁለት ልጆች በማደሪያው ድንኳን ካህናት ሆነው ያገለግሉ የነበረ ቢሆንም የአምላክን ሕግ አልታዘዙም። ትንሹ ሳሙኤል ግን ከእነሱ የተለየ ነበር፤ በመሆኑም ይሖዋ አነጋገረው።
ትምህርት 38
ይሖዋ ለሳምሶን ታላቅ ኃይል ሰጠው
ይሖዋ፣ ሳምሶን ከፍልስጤማውያን ጋር እንዲዋጋ ሲል ኃይል ሰጠው፤ ሳምሶን የተሳሳተ ውሳኔ ሲያደርግ ግን ፍልስጤማውያን ያዙት።
ትምህርት 39
የመጀመሪያው የእስራኤል ንጉሥ
አምላክ ለእስራኤላውያን የሚመሯቸው መሳፍንት ሰጥቷቸው የነበረ ቢሆንም እስራኤላውያን ንጉሥ እንዲሾምላቸው ፈለጉ። ሳሙኤል ሳኦልን የመጀመሪያው ንጉሥ እንዲሆን ቀባው፤ በኋላ ግን ይሖዋ ሳኦልን ትቶ ሌላ ንጉሥ ለመሾም ወሰነ። ለምን?
ትምህርት 40
ዳዊት እና ጎልያድ
ይሖዋ ቀጣዩ የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን ዳዊትን መረጠው፤ ዳዊት ያደረገው ነገር እሱ ንጉሥ እንዲሆን መመረጡ ተገቢ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
ትምህርት 52
የይሖዋ የእሳት ፈረሶችና የጦር ሠረገሎች
የኤልሳዕ አገልጋይ፣ ኤልሳዕ ‘ከእነሱ ጋር ካሉት ከእኛ ጋር ያሉት ይበልጣሉ’ ያለው ለምን እንደሆነ ማስተዋል ቻለ።
ትምህርት 54
ይሖዋ ዮናስን በትዕግሥት አስተማረው
አንድ የአምላክ ነቢይ በትልቅ ዓሣ የተዋጠው ለምንድን ነው? ከዓሣው ሆድ የወጣውስ እንዴት ነው? ይሖዋ ዮናስን ምን አስተማረው?
ትምህርት 59
ይሖዋን የታዘዙ አራት ልጆች
አይሁዳውያን ወጣቶች በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነጾር ቤተ መንግሥት ውስጥ በነበሩበት ጊዜም ጭምር ለይሖዋ ታማኝ ለመሆን ወስነው ነበር።
ትምህርት 73
ዮሐንስ ለመሲሑ መንገድ አዘጋጀ
ዮሐንስ ካደገ በኋላ ነቢይ ሆነ። ዮሐንስ መሲሑ እንደሚመጣ ያስተምር ነበር። ሕዝቡ ዮሐንስ ያስተማረውን ትምህርት ሲሰሙ ምን አደረጉ?
ትምህርት 77
ውኃ ልትቀዳ የመጣችው ሳምራዊት ሴት
አንዲት ሳምራዊት ሴት ኢየሱስ ሲያነጋግራት በጣም ተገረመች። ለምን? ኢየሱስ ለሌላ ለማንም ሰው ያልተናገረውን ምን ነገር ነገራት?
ትምህርት 78
ኢየሱስ የአምላክን መንግሥት ምሥራች ሰበከ
ኢየሱስ አንዳንድ ደቀ መዛሙርቱን “ሰው አጥማጆች” እንዲሆኑ ጥሪ አቀረበላቸው። ከጊዜ በኋላም ከተከታዮቹ መካከል 70ዎቹን ምሥራቹን እንዲሰብኩ አሠለጠናቸው።
ትምህርት 79
ኢየሱስ ብዙ ተአምራት ፈጽሟል
ኢየሱስ በሄደበት ቦታ ሁሉ፣ የታመሙ ሰዎች ከበሽታቸው እንዲያድናቸው ወደ እሱ ይመጡ ነበር፤ እሱም ሁሉንም ፈውሷቸዋል። አንዲትን የሞተች ልጅ እንኳ አስነስቷል።